አራት ኪሎ አከባቢ ከሚገኘው ቱሪስት ሆቴል በረንዳ ላይ የቀን ፀሐይ በቡና እያወራረድን በጋዜጣና  

በመጽሔት ከሸኘን በኋላበእግራችን እየተራመድን ልክ ትምሕርት ሚንስቴር ሕንፃጋ ሥንደርሥ “ሳምኬት” ቆም እንድንል ካዘዘችኝ በኋላ አይኖTን አራት _ ኪሉ አደባባይ መሃል ላይ ለአርበኞች መታሠቢያነት ወደተሠራው ሃውልት ላይ ልካ

እዚህ ሃውልት ጫፍ ላይ ያለውን ሠዓት አየኸውጥያቄ ነው ከእርሷ ለእኔ  ብዙ ጊዜ ለእንደዚህ አይነት ነገሮች ልዩ

 ትኩረት ትሠጣለች ይኸውም የትምህርቷ ዝንባሌ የሚፈጥረው ልዩ ስሜት መስሎ ሥለሚሰማኝ ለነገሮቹ ያለኝ ምልከታ የተለየ ቢሆንም እርሷ የምትሠጠውን ትንተና (Analysis) ለመስማት ሥል ልዩ ትኩረት አድርጌ ሕሊናዬን ወደ ነገሮቹ እሠበስባለሁ ዛሬም እንደዚያው መስሎኝ… ሃውልቱ ጫፍ ላይ የሚገኘውን ሠዓት ለግማሽ ደቂቃ ያህል ካስተዋልኩ በኋላ 

አዎን አየሁት ግን ሰባት ሰዓት ላይ ብቻ የቆመ ይመስላል  ትክክል” ፈጠን ብላ  ልክ ነህ ሠዓቱ ሃያ አራቱም ሰዓት ላይ ብታየው ሰባት ሰዓት ላይ እንደቆመ ነው፡፡

                                   አልፎ ሂያጅ አላፊ አግዳሚዎች የሁለታችን ሰዓቱ ላይ ማፍጠጥ አስገርሟቸው ጤነኛ ናቸውበሚል ሁኔታ ከገረመሙን በኋላ አይኖቻቸውን ወደሀውልቱ መለስ እያደረጉ የፌዝ ሳቅ  አሳይተውን መንገዳቸውን ይቀጥላሉ፡ ምናልባትም “ሲያሳዝኑእያሉ እኔም የሰዓቱ ከሰባት በላይም ሆነ በታች አለመንቀሳቀሱ የተቃወሙጊዜ ኢትዮጵያን በወረረጣሊያን አርበኞች በዱር በገደል የነበሩት በድል አድራጊነት ወደ መሀል ከተማ የገቡበትና የተሰባሰቡበት ሰዓት ሰባት ሰዓት መሆኑን” የማውቀውን በመጠኑ መለስኩ፡፡

 እርሷም አይኖቼን በአይኖቿ ለተወሰኑ ቅዕበታት በትኩረት አይታ የቀኝ እጇን መዳፍ በግራ እጆቼ መዳፍ ጡስጥ አቆላልፋ የመገናኛን አቅጣጫ የፊታችንን መንገድ አየር እየሰነጠቅን “ልክ ነህ ለእኔ ግን ከዚያም በላይ ትርጉም ይሰጠኛልከዚያ በላይ የሆነ አንቺ ምን አይነት ትርጉም አገኘሽበት መልሼ እኔ ጠየቅኩኝ


ምንም እንኳን ሰዓቱ ሰባት ላይ እንዲቆም መደረጉ አርበኞቹ ሀገራችንን አናስደፍርምየሚያገኘንም ሁሉ አይገድለን
ፈፅሞ ብለው እንቢታቸው!አሻፈረኝ ባይነታቸው በድል መሽገው ከየነበሩበት ሥፍራ ወደ መሀል ከተማ ተመልሰው
የተሰባሰቡበት መታሰቢያ ቢሆንም የዚህ ሰዓት “ሰባት” ላይ መቆም ግን ከዚያ በኋላ በመጡት ትውልዶች ላይ   
 ትዝብትና ሥላቅ ይመስለኛል"

ምን አይነት ትዝብት ምንስ አይነት ስላቅ

ምናልባት የምነግርህ ነገር የግሌ አመለካከት ሊሆን ይችላል ለሌላ ሰውም ትምህርት ላይሰጥ ይችላል ቢሆንም ግን ጠያቄዬ አንተ ነህና ነግርሃለሁ"

እባክሽን

ለእኔ ሀውልቱ ላይ ያለው ሰዓት እንደቆመ መቅረቱ በሀገራችን ከዚያ በኋላ ኢትዮጵያዊ ትርጉም ያለው ሥራ አለመሰራቱን እና እንዲሁም ደግሞ ተሰርቶ የነበረው የደጋጎቹ ምልክት ጠፍቶ መቅረቱን የሚናገር የሥላቅና የትዝብት ምልክት ነው ሰነፎችየሚወቅስ"

ከዚህ በኋላ በሁለታችን መሀል የነበረው ወግ ምንም አይነት ድምጽ የሌለው ስሜታዊ መግባባት ብቻ ነበር፡፡

የአራት ኪሎ ሀውልት ( አርበኞች ሀውልት)